Blog

አማጭ-አዋጭì

ትዳር ከሚመሰረትበት መንገድ አንዱ በአማጭ በኩል የሚደረግ መጣመድ (matchmaking)  ነው። “እከሌና እከሊት ቢጋቡ ጥሩ ይጣነዳሉ” ብሎ/ላ በጥሩ መንፈስ የተነሳሳ ሰው ለሁለቱ ተጣናጆች እንዲተያዩ፣ እንዲተዋወቁ ሁኔታውን ሲያመቻቹላቸው ማለት ነው። በቅን ልቦና ተነሳስተው እራሳቸውን የአማጭ መንበር ላይ ያስቀመጡ ሰዎችን የማደንቅ ነኝ፤ እኔ በግሌ፡፡

The Boundaries Within

I often find myself pondering; where does my boundary end, and where do others begin? There is an invisible yet palpable line within each of us dictating how we navigate our understanding of ourselves, and those around us. Without a clear grasp of where this boundary lies, misunderstandings and emotional distress is inevitable.

አልሞተችም!

በዚህች ምድር ላይ ስንኖር መቼስ ይሆናል ካልነው ይልቅ አይሆንም ያልነው እየሆነ ማየትን ተለማምደነዋል፡፡ ይሄ ግጥምጥሞሽ ሲደጋገም ነው ከእኛ በላይ ሌላ ትልቅ አዛዥ ናዛዥ፣ ተቆጣጣሪ እና ወሳኝ ኃይል እንዳለ የማንጠራጠረው(የማልጠራጠረው በሚለው ይታረምልኝ)፡፡ ለነገሩ እኮ ሕይወትም የሚያጓጓው የገመትነው ሳይሆን ቀርቶ በድንገቴ (surprise) በመታጀቡ ነው፡፡ ታድያ ክፉውን ድንገቴ ያርቅልን!

Double it and Give it to the Next Person

Like chivalry, kindness may be dead—or at least on the brink of dying. In today’s age, everybody is so busy trying to be somebody that we’ve forgotten how to be in the moment and appreciate the basic nature of our being. From childhood to adolescence to adulthood, kindness has become a luxury we can’t afford to trust.

አትተኙ!

እስቲ ስንቶቻችሁ ናችሁ “የሕይወቴ ቅኝት” የሚለውን መጽሐፍ ያነበባችሁ? ያላነበባችሁ እንግዲህ ተዋውሳችሁ አንብቡ ምክንያቱም ሁለተኛ እትም ለማሳተም “እቁብ ግቡልኝ?” ብዬ ጓደኞቼን በዚህ ዘመን አላስቸግርም፡፡ ድሮ የእኛ ዘመን፣ የእነሱ ዘመን ስንል አስር ወይንም ሃያ ዓመት ልዩነት እየፈለግን ነበር፤ ምክንያቱም ለውጦች አዝጋሚ (evolutional change) ናቸዋ፡፡ አሁን እኮ ዘመን ወደ ሳምንት ተቀይሯል መሰለኝ ባለፈው ሳምንት የነበረ ዛሬ ተለውጦ ታገኙታላችሁ፡፡ ነገር ሁሉ እንደቤት አስቤዛ ተለዋዋጭ ሆኗል፡፡ የዛሬ ሦስት ዓመት በኤውብ እቁብተኞቼ ድጋፍ አሳትሚያለሁ፡፡ እና ኑሮ ቀልብ ባሳጣበት እና አንባቢ በጠፋበት በዚህ ዘመን ወደ ማተምያ ቤት አልሄድም ለማለት ነው፡፡ ለማንኛውም መጽሐፌን ያነሳሁላችሁ ከዚያ ውስጥ አንዱን ሰበዝ መዝዤ ላወራላችሁ ፈልጌ ነው፡፡

ትዳራችን ኮሽታ የለውምì

ድሮ ወደ ኮሌጅ ልገባ ስል ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ወደ ኮሌጅ ለመሄድ የሚያዘጋጅ መጽሐፍ ነው ተብሎ የታመነበትን የሲሳይ ንጉሱ ድርሰት የሆነውን “ሰመመን” አንብቤ እንድዘጋጅ ያደረጉትን የጓደኛዬ የገነት ወንድሞች በሕይወቴ ክብር መዝገብ ላይ ጽፌአቸዋለሁ፡፡ አስባችሁታል ገና ዩኒቨርስቲውን ዋና በር ስትረግጡ በስህተትም ተብላችሁ የማታውቁትን “እንዳንቺ አይነት ቆንጆ ሴት በዚህ ምድር አይቼ አላውቅም!” የሚሏችሁ ሲኒየር ተማሪዎች ሙድ እየያዙባችሁ እንደሆነ አይገባችሁም ነበር እኮ፡፡

The Beauty of Being Unfinished

The constant need for completeness engulfs us in our daily lives. Who are we? Give us something – anything – what’s our label? Between ‘What’s your name?’ and ‘What do you do?’ lies a pre-determined soliloquy that quenches a curious stranger’s thirst, while we repeatedly tell ourselves what makes us, US. It is a tradition, a universal law to be categorized; it has been done since the beginning of time.

እርጉዟን ማን ይቅጠራት!?

እርጉዟን ማን ይቅጠራት!? Image source: https://www.pngegg.com/en/png-besfc/download አንዳንድ የጦፉ ክርክሮች በአንድ ወገን አሸናፊነት ወይም አሳማኝነት ሳይቋጩ ሲቀሩ እንዴት ያንገበግበኛል መሰላችሁ፡፡ በጓደኛሞች ወይም በቤተሰብ መሀከል የሚደረግ ክርክር ወይም ቃሉን የተሻለ ለማድረግ ጭውውት …

እርጉዟን ማን ይቅጠራት!? Read More »

ጆሮም እንደ ዓይን መዝጊያ ቢኖረው?!

የሰውነት አካላችን በቅንጅት የሚሰራው ስራ እኛን እኛ ያደርገዋል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ለነገሮች ተጋላጭ የሚያደርገን ፈልገን ሳይሆን ሳንፈልግ ወይንም ከአቅም በላይ በሆነ ክስተት ነው፡፡ ለምሳሌ አንድ ቦታ ሄደን ለተከሰተው ክስተት እግራችን ፈቅዶ ባይሄድ ላናይ ላንሰማ እንችል ነበር፡፡ በሄድንበት ቦታ ዓይናችን “ይሄን ማየት አልፈልግም” ብሎ ከጨፈነ ያንን ክስተት ባለማየት እንተርፋለን ማለት ነው፡፡ እጃችንም ከመንካት ከታቀበ ታቀበ ነው፡፡ ብቻ በአብዛኛው የሰውነታችን ክፍል እምቢ የማለት መብት እስኪኖረው ድረስ ነው የተሰደረው፡፡ አፍንጫ እንኳን እድሜ ለኮቪድ አይባልም እንጂ ልብስ ተሰፍቶለታል፡፡