ተጋልጠናል!
ማህበራዊ ሚዲያ (social media) ተጠቃሚ ከሚባሉ ሰዎች አንዷ ነኝ፡፡ በተለይ ፌስቡክ በጣም ጊዜ ካጣሁ እንኳን በቀን አንዴ ገብቼ ትንሽ መልእክት እጽፋለሁ፤ የሌሎችን ጽሑፎች አነባሁ፤ ሀሳብ እሰጣለሁ፣ እቀበላለሁም፡፡ ብዙ ሰዎች ፌስቡክን የስራ-ፈት ሚዲያ አድርገው ስለሚቆጥሩት እንደተዉት ሲናገሩ እሰማለሁ፡፡ እኔ ደግሞ በተቃራኒው ምንያህል እየተጠቀምኩበት እንደሆነ ቤቴ ይቁጠረው፡፡









