Fitsum Atnafekework

እየሞከርኩ ነው!

ሰሞኑን በጣም በብዙዎች የታየ፣ የተወደደ እና መነጋገርያ የሆነ ቪዲዮ ለዛሬ ጽሑፌ ከነርእሱ መነሻ ሆኖኛል፡፡ ላላያችሁት ግን ትንሽ ስለቪዲዮው ልንገራችሁ፡፡ አንድ አከራይ ተከራዩን መንገዱ ላይ ጠብቆ የቤት ኪራይ ሳይከፍል በመዘግየቱ እንዲከፍል ሲያስታውሰው ግራ የተጋባው ተከራይ ምርር ብሎ ሳይከፍል የዘገየበትን የተደራረበ ችግር የሚናገርበት አባባል ነው፤ “እየሞከርኩ ነው!” ማለቱ፡፡ ሁላችንም ችግሮቻችንን ለማሸነፍ እየሞከርን ነው፡፡ ግን ደግሞ ችግርን የሚቀርፍ ወይንም ፈቀቅ አድርጎ እና እፎይታ የሚያስገኝ ሙከራም እያደረግን ለመሆኑ ብዙዎቻችን እርግጠኞች አይደለንም፡፡ ታድያ “ሙከራችን ምን አይነት ቢሆን ነው?”

እየሞከርኩ ነው! Read More »

በየዓመቱ ማግባት!

ዘመን በተቀየረ ቁጥር አዲስ ዓመትን ተከትሎ ብዙዎቻችን “ይሄን አዲስ ዓመት በአዲስ ጉልበት እና እቅድ ነው የምኖረው፤ እስካሁን ያላሳካሀሁትን ሁሉ ነው የማሳካው…ወዘተ እንላለን፡፡ የዘንድሮ ዘመን እንደሆነ ገባ ብለን ሳንጨርስ አልቆ ቁጭ ነው የሚለው፡፡ ቆይ የድሮ አመት 365/6 ቀናት ነበሩ አይደል!? አሁንም ግን ያው ነው ወይንስ ተኝተን ስንነቃ የሚሰርቀን የማናውቀው መንፈስ አለ!? ይሄ ጥያቄ የሁላችንም ስለሚመስለኝ እና መልሱን ማናችንም ስለማናውቀው እዘለዋለሁ፡፡

በየዓመቱ ማግባት! Read More »

በጋመ ምጣድ ለመጋገር ወረፋ አንያዝ!

አቤት የድሮ ጉርብትና እኮ ብዙ ደሳስ የሚሉ ትውፊቶች ነበሩት። ማህበራዊ ኑሮው በተለይ ዳግም ላይመለስ የጠፋ እንደ ትርክት ለልጆቻችን የምናወራው ለእኛ ብቻ ትዝታው የሚያስደስተን:፡ ለምሳሌ እንዲህ እንደአሁኑ በከተማችን ብዙ የኤሌክትሪክ ምጣደች በየቤቱ ባልነበሩበት ዘመን የጋራ የሆኑ የጭስ ኩሽናዎች ነበሩ፡፡

በጋመ ምጣድ ለመጋገር ወረፋ አንያዝ! Read More »

ወንዶች እና ቀለበት

በስራዬም በትምህርት ቤቶቼም ያፈራኋቸው ድንቅ ድንቅ የሁኑ የወንድ ጓደኞች አሉኝ፡፡ ወንዶች ለጓደኝነት በጣም ይመቻሉ፡፡ ጓደኝነት ስል ግልጽ ለማድረግ ጾታዊ ንክኪ የሌለበት ጓደኝነት ወይንም በተለምዶ ወንድም ጓደኛ ማለት ነው፡፡ በተለይ በአንድ ርእሰ ጉዳይ ላይ ለመወያየት ያወቁትን እና የገባቸውን በግልብ ያለማለባበስ ለማስረዳት ምንም ወደኋላ አይሉም፡፡ እንደዚያ ማለቴ ደግሞ ሴት ጓደኞች አይመቹም እያልኩ እንዳልሆነ ያሉኝ የሴት ጓደኞች ብዛት ምስክር ነው፡፡ አሁን ለማውራት የፈለግኩት ስለግልጽ ውይይት ነው፡፡ በተለይ እኛ ሴቶች ብዙ ነገር እንደ ነውር (taboo) እየተቆጠረብን ሀሳባችን ተቆነጣጥሮ የሚቀርብበት ይበዛል መሰለኝ፤ ማለቴ መሰለኝ ስል ያው ጥርጣሬ ነው፡፡ እና ግልጽ ውይይት የምንፈራው ወደንና ፈቅደን ሳይሆን ማህበረሰቡ የሰራን በሽፍንፍን እንድንወያይ ነው ለማለት ነው፡፡

ወንዶች እና ቀለበት Read More »

Office Politics Recap

On November 1st, AWiB members attended an insightful seminar on “Office Politics,” led by Fitsum Atnafework Kidanemariam. The session delved into the dynamics of workplace relationships, the role of formal and informal communication channels, and how understanding organizational politics can empower individuals to navigate professional environments more effectively.

Office Politics Recap Read More »

እያለን የለንም!

እያለን የሌለው ምን ይሆን ብላችሁ ከጠየቃችሁኝ ካለን ነገር ብጀምር በጣም ብዙ ነገር አለን፡፡ ብዙዎቻችን በተወሰነ መልኩ ትምህርት ቤት የሄድን፣ በተለያዩ ስራዎች እና ንግድ ላይ የተሰማራን፣ ከሰዎች ጋር የምንኖር እና የምንሰራ፣ ከሰዎች ልምድም እውቀትም የምንጋራ የምንማማር ሰዎች ነን፡፡ ብዙዎቻችን አእምሮ አለን፤ የምናስብበት፣ የምንተሳሰብበት፣ የምናሰላበት፣ የምንሰላበት፡፡ ከአእምሮ በተጨማሪ የስሜት ሕዋሳቶች አሉን፤ አካባቢያችንን የምናይበት፣ የምናዳምጥበት (ካዳመጥን…በኋላ እመለስበታለሁ)፣ ሚዛን የምንጠብቅበት፣ የምንዳስስበት፣ የምንንቀሳቀስበት፣ የምንቀምስበት እና የምንለይበት፡፡ እነዚህ የግል ንብረቶቻችን ሲሆኑ እንደማህበረሰብ ደግሞ ባህል፣ ኃይማኖት፣ ማህበራዊ ኑሮ፣ ሀገር፣ መንደር፣ ወዘተ አሉን፡፡ አንድ ሰው በዚህ ሁሉ መኖር ውስጥ ታድያ እንዴት ነው አቅም እና አቋም እንደሌለው ሆኖ የሚገኘው!?

እያለን የለንም! Read More »

የአበባየሽ ወይ ገራሚ እይታ!

መስከረም አንድ ቀን የሚከበረው የኢትዮጵያ አዲስ አመት የአንድነት አውድአመት ነው፤ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ዘር እና ኃይማኖት ሳይለይ የሚያከብረው እና በደስታ የሚቀበለው፡፡ ሁላችንም ልጅ አዋቂው እንኳን ለ2018ዓ.ም. በሰላም ደረሰኝ የምንባባልበት ትልቅ ቀን ነው (በዚሁ እንኳን አደረሰን ብያለሁ!)፡፡ እለቱም እንቁጣጣሽ ተብሎ በተለይ ታዳጊ ሴቶች ልጆች “አበባ አየሽ ወይ!” ብለው እየዞሩ ይጨፍራሉ፤ ሳይርቁ በጎረቤቶች እና በሚያውቋቸው ሰዎች ቤቶች፡፡ ታድያ ዛሬ በዚህ ጉዳይ የሚያስወራኝ ገጠመኝ ስለኖረኝ እንጂ አዲስ አመትማ ሁላችንም የምናውቀው እና የምናከብረው ነውና እያስተዋወቅኳችሁ እንዳልሆነ ይሰመርበት፡፡

የአበባየሽ ወይ ገራሚ እይታ! Read More »

አትሞገሽ ያላት ፍጡር!

ሰው የሚለው ስያሜ ውስጥ ሁለታችንም አለን፤ ሴቶችም ወንዶችም፡፡ ነገር ግን ለአገላለጽ ስንጠቀመው ሰው የሚለውን ስያሜ በወንድ እንጠቀልለውና ሴቶችን እንዘላቸዋለን፤ ማለቴ እኛ ሴቶች እንዋጣለን፡፡ ለምሳሌ “ሰው መጣ” ስንል የመጣችው/የመጣው ሴት ወይንም ወንድ ሊሆን ይችላል፡፡ ያኔ ነበር ከመነሻው “ለምን?” ብለን መጠየቅ የነበረብን፡፡ ምክንያት ካላችሁኝ ኋላ ላይ ልመለስበት፤ አይሻልም? ወይንም ሳልመለስም ቢሆን ሀሳቤ ይገልፀው ይሆናል፡፡ ከዚያ በፊት ግን እንኳን ለአድዋ የድል መታሰብያ እና ለማርች የሴቶች ወር አደረሰን! ወቅቱ የአድዋ ድል የሚዘከርበት እና ተከትሎም የማርች ወር የሴቶች እኩልነት ይረጋገጥ በሚል ብዙ መድረኮች የሚዘጋጁበት እና እኛም የምንሳተፍበትም አይደል፤ እኮ!

አትሞገሽ ያላት ፍጡር! Read More »

አማጭ-አዋጭì

ትዳር ከሚመሰረትበት መንገድ አንዱ በአማጭ በኩል የሚደረግ መጣመድ (matchmaking)  ነው። “እከሌና እከሊት ቢጋቡ ጥሩ ይጣነዳሉ” ብሎ/ላ በጥሩ መንፈስ የተነሳሳ ሰው ለሁለቱ ተጣናጆች እንዲተያዩ፣ እንዲተዋወቁ ሁኔታውን ሲያመቻቹላቸው ማለት ነው። በቅን ልቦና ተነሳስተው እራሳቸውን የአማጭ መንበር ላይ ያስቀመጡ ሰዎችን የማደንቅ ነኝ፤ እኔ በግሌ፡፡

አማጭ-አዋጭì Read More »

አልሞተችም!

በዚህች ምድር ላይ ስንኖር መቼስ ይሆናል ካልነው ይልቅ አይሆንም ያልነው እየሆነ ማየትን ተለማምደነዋል፡፡ ይሄ ግጥምጥሞሽ ሲደጋገም ነው ከእኛ በላይ ሌላ ትልቅ አዛዥ ናዛዥ፣ ተቆጣጣሪ እና ወሳኝ ኃይል እንዳለ የማንጠራጠረው(የማልጠራጠረው በሚለው ይታረምልኝ)፡፡ ለነገሩ እኮ ሕይወትም የሚያጓጓው የገመትነው ሳይሆን ቀርቶ በድንገቴ (surprise) በመታጀቡ ነው፡፡ ታድያ ክፉውን ድንገቴ ያርቅልን!

አልሞተችም! Read More »

Scroll to Top