ስለ ሴት መልካም አባባሎች!?
አንዲት የኤውብ ቤተሰብ የሆነች እህት ስልክ ደወለችልኝ እና “እስቲ ስለ ሴት የተተረቱ አዎንታዊ አባባሎች ንገሪኝ?” አለችኝ፡፡ ጥያቄው ቅጽበታዊ ቢሆንም ጊዜ ወስጄ ባወጣና ባወርድ በቶሎ ሊመጣልኝ አልቻለም፡፡
ስለ ሴት መልካም አባባሎች!? Read More »
አንዲት የኤውብ ቤተሰብ የሆነች እህት ስልክ ደወለችልኝ እና “እስቲ ስለ ሴት የተተረቱ አዎንታዊ አባባሎች ንገሪኝ?” አለችኝ፡፡ ጥያቄው ቅጽበታዊ ቢሆንም ጊዜ ወስጄ ባወጣና ባወርድ በቶሎ ሊመጣልኝ አልቻለም፡፡
ስለ ሴት መልካም አባባሎች!? Read More »
አንድ ቀን እለት አንድ ሆስፒታል ውስጥ ቁጭ ብዬ ተራ እየጠበቅሁ ሳለሁ ዘለግ ያለች ሴት የተጫማችውን ነጠላ ጫማ በድካም ስሜት እየጎተተች መጥታ ፊት ለፊቴ ተቀመጠች፡፡ ፊቷ አዲስ አልሆነብኝም፤ ግን ደግሞ እሷ ፊት ላይ ምንም “የት ነው የማውቃት?” መደናገር ስላላየሁባት የመልክ መመሳሰል አድርጌ ወስጄው በዝምታ እያለሁ ለየት ያለው ስሟ ከነአባቷ ሲጠራ ግምቴ ልክ እንደነበረ አመንኩ፡፡
ምን ሆነ መሰላችሁ! ሰሞኑን አንድ የቤተሰብ የምሳ ግብዛ ላይ አንድ ወጣት በትህትና ሲያስተናግድ ቆይቶ ለመሄድ ሊሰናበት ሲል ግብዣውን ያዘጋጁት ታላቅ ሰው ልጁን ለታዳሚዎች ማስተዋወቅ ፈለጉ፡፡ በጣም ጥሩ ልብ ያለው ልጅ መሆኑን፣ የዩኒቨርስቲ ምሩቅ መሆኑን እና ድግሱንም በደንብ ያገዘ መሆኑን አስተዋወቁና እስቲ እራስህን አስተዋውቃቸው በማለት እድሉን ሰጡት፡፡
ማህበራዊ ኃላፊነት እና የእራስ ኃላፊነት Read More »
ማህበራዊ ሚዲያ (social media) ተጠቃሚ ከሚባሉ ሰዎች አንዷ ነኝ፡፡ በተለይ ፌስቡክ በጣም ጊዜ ካጣሁ እንኳን በቀን አንዴ ገብቼ ትንሽ መልእክት እጽፋለሁ፤ የሌሎችን ጽሑፎች አነባሁ፤ ሀሳብ እሰጣለሁ፣ እቀበላለሁም፡፡ ብዙ ሰዎች ፌስቡክን የስራ-ፈት ሚዲያ አድርገው ስለሚቆጥሩት እንደተዉት ሲናገሩ እሰማለሁ፡፡ እኔ ደግሞ በተቃራኒው ምንያህል እየተጠቀምኩበት እንደሆነ ቤቴ ይቁጠረው፡፡
እድገታችን የሚለው ቃል ሁላችንንም በሀሳብ በየአቅጣጫው እንደወሰደን አልጠራጠርም፡፡ የቱን እድገት ይሆን ደግሞ ዛሬ የምታወራልን፤ የሀገራችንን? የልጅነታችንን? የድርጅታችንን? እድገት በየፈርጁ በአእምሯን ውስጥ ተመላለሰ አይደል! እኔ ግን ማውራት የፈለግኩት የስራ ቦታ እድገት (promotion) ነው፡፡
ስኬታማ ሴቶች የሆኑትን የሆኑት ብዙ ወድቀውና ተነስተው ነው! ለነገሩ ሴቶች ብቻ ሳይሆኑ ወንዶችም ጭምር፡፡ የእኔ ነገር በቀላሉ ሰዎች ብዬ እኮ ማጠቃለል እችል ነበር አይደል! ግን ማውራት የፈለግኩት ስለስኬታማ ሴቶች ገመና ነውና ነው፡፡ ወንዶች ስኬታማ ሲሆኑ ጎበዝ ነው፣ ባለሀብት ነው፣ ታድሎ፣ ከምን ተነስቶ ይሆን እዚህ የደረሰው፣ ወዘተ የመሳሰሉት እሱና እሱ ላይ ያተኮሩ አስተያየቶች እና አድናቆቶች ሲሰጡ ከመስማት ያለፈ ብዙም ስለ እሱ (ስለስኬታማው ሰውዬ) ግላዊ ማንነት ገፋ ተደርጎ ሲጠየቅ ወይንም ሲወራ አጋጥሞኝ አያውቅም፡፡ ቢጠየቅም ለአመል እንጂ ያንን ያህል እርቀት አይኬድም፡፡
በሕይወቴ ብዙ የመጀመርያ እና አስደናቂ የሚባሉ ገጠመኞች ሞልተውኛል፤ በአብዛኛው ድንቅ የሚባሉ ሲሆኑ በተቃራኒውም ድንቅ ያልሆኑ ገጠመኞች አሉኝ፡፡ መጀመርያ ድንቅ ያልሆነውን አንዱን ልተርክላችሁ፡፡ ለረዥም ዓመታት የሰራሁበት እና በተለይ በወጣትነቴ ብዙ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ በማገልገል የምታወቅበት መሥሪያ ቤት በወቅቱ መሀከለኛው የአመራር ደረጃ ላይ ለነበርነው ኃላፊዎች በአውሮፓ ሀገራት የልምድ መጋራት እና የአጭር ስልጠና እድል ይሰጥ ነበር፡፡
እንደ ሁኔታው! በአንድ ወቅት እሰራበት የነበረ አንድ ዓለም አቀፍ ግብረ ሰናይ ድርጅት የመዋቅር ለውጦችን አደረገ እና ለረዥም ዓመታት ያገለገሉትን ሰራተኞች የአገልግሎት ዘመን ያላማከለ ስለነበር እጅግ አስቆጣቸው፡፡ በወቅቱ የነበረው የድርጅቱ ዋና
መቼስ እኛ ሰዎች ስንባል አንዱ መተዳደርያ ደንባችን በትንሹም በትልቁም ብስጭትጭት ማለት፣ መነጫነጭ፣ ማማረር የመሳሰሉት ጥቃቅን እና አነስተኛ ባህርያት ናቸው፡፡ እርግጥ ነው ስሜትን መግለጽ ሰውኛ ነው፡፡ ግን ደግሞ የእኛ ልምምድ ትንሽ በዘት ይላል፡፡
የዛሬ ጽሑፌ መነሻ ሰሞኑን ከድሮ መ/ቤት ባልደረባዬ የተደወለልኝ ስልክ ነው፡፡ ይህቺ የሥራ ባልደረባዬ ደውላ ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ በተለያየ ሚዲያ እያየችኝ እንደሆነ እና እድገቴ እንደሚያስገርማት በመግለጽ አድናቆቷን ካርከፈከፈችልኝ በኋላ ጨዋታውን አደራነው፡፡ አመስግኛት ሳበቃ ስለቤተሰብ፣ ስለ ሥራ ወዘተ ተጠያየቅን፤ ወግ ነውና፡፡ ይህች የቀድሞ የሥራ ባልደረባዬ ስትደውልልኝ ተጠንቅቄ ነው የማናግራት፤ ከቀድሞ ባህርይዋ በመነሳት፡፡ የፈለገውን ዓመት ፈጅቶ ባገኛት ምንም የተሻሻለ የባህርይ ለውጥ የማይታባት ናት፡፡ አሁንም እዚያው ከእኔ በፊት ተቀጥራ የምትሰራበት መ/ቤት እየሠራች መቆየቷ ነው መሰለኝ የተግባቦት ስልቷ አልተለወጠም፡፡ የዚያ መ/ቤቱ ብቻ ሳይሆን የባህርይዋም ታማኝ እና ቅን አገልጋይ እንበላት ይሆን!? በደወለችባቸው ወይም ባገኘኋት አጋጣሚዎች ሁሉ ታጉረመርማለች፡፡